የ2017 የከተራ በዓል በዋድላ ኮን ከተማ መከበር ጀምሯል።
30-04-2026 21:50pmየ2017 የከተራ በዓል በዋድላ ኮን ከተማ መከበር ጀምሯል። በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ዋድላ ወረዳ በኮን ከተማ የከተራ በዓል እየተከበረ ይገኛል። አራት ታቦታት በአንድ ላይ በተዘጋጀላቸው ቦታ የሚያድሩ ሲሆን እነርሱም ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ፣ ታች መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፣ ላይ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ እና አዳሌ መስክ ቅድስት ልደታ ናቸው። ታቦታቱ በወረዳው ቤተ ክህነት ሠራተኞች፣ በአድባራት ካህናት፣ በሊወቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ በሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች፣ በማኅበረ ቅዱሳን ኮን ወረዳ ማእከል አባላት፣ በበገና ዘማሪያን፣ በበጎ ፈቃድ ወጣቶች እና ምእመናን በዝማሬና በእልልታ ታጅበው ወደ ተዘጋጀላቸው ቦታ በክብር ገብተዋል።



